Sunday, March 8, 2009

ጥላቻን ማስፋፋት ዓይነተኛ የወያኔ መመርያ ነዉ!

የወያነ ትግራይ ገበና ማሕደር ጥላቻን ማስፋፋት ዓይነተኛ የወያኔ መመርያ ነዉ! ጌታቸዉ ረዳ “ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ” ዘረኛነት በተደጋጋሚ የተነጋገርንበት ጉዳይ ነዉ። በቅርቡ ዛሬ ዛሬ ደግሞ በተቃዋሚነት ቆመናል የሚሉ የዓረና እና የጉንበት 7 ደጋፊዎች እና የብረቱካን ፓርቲ ደጋፊ አባላት ስለ ወያኔ የገበና መሕደር አንስተን በዘገብን ቁጥር “እጅ እጅ” ያላቸዉ ይመስላሉ። እነሱ ብቻም አይደሉም ጉዳዩን አንስተን በተከራከርንባቸዉ ወቅቶች፤ ብዙ የድርጅቱ አባላት እና አቁዋማቸዉ ነጥሮ ያልወጣ የድርጅቱ “ነበር” አባላት እና አዳዲስ አባላት አፍቃሬ-ወያኔ“የእርጎ ዝምቦች” ክርክራችንን ለማጣጣል ብዙ የስም ማጥፋት ዘመቻዎች አካሂደዉብናል። በቅርቡም በዚህ “ዌብ ሎግ/በራሴ ዌብ ሎግ” እና በኢትዮፓትሪዮትስ . ካም” ሰሌዳ ዉስጥ ቀርቦ በነበረዉ “የወያኔ ትግሬዎች እና የዓድዋ ድል እይታ”ን በተመለከተ በግል “ኢሜይል” በመላክ “ወያኔ ጸረ አማራ ገዢዉ መደብ እንጂ ጸረ አማራ አልነበርም” ሲሉ “በዚህ ጉዳይ አንስተን ስንከራከር- እኔ ታጋይ እስከነበርኩበት ጊዜ ድረስ ጸረ አማራ ቅስቀሳ ወይንም ዘፈን አልሰማሁም” በማለት ወያኔያቸዉን የመከላከል በሽታ ከቶ ምንም ያልተዋቸዉ ሰዎች ዛሬም ስላሉ - እዉነት እና ንጋት እያደር ይጠራል እንደተባለዉ፣ ምንም ያህል ቢደበቁም ከታሪክ ተደብቆ ለረዥም ጊዜ ማላገጥ ስለማይቻል፣ በራሳችን ክርክር ከመሞገት ይልቅ “ድርጅቱን በግምባር ቀደም በመሰረተዉ በዶ/ር አረጋዊ በርሄ” ብዕር ማስረጃችንን በማቅረብ (ማሌሊት ዘላሊት) ወይንም “ከማገብት እስከ ህወሓት- ጠባብ ብሔረተኝነት ያመናመነዉ ትግላችን” ከሚለዉ ሰነድ ከረዥሙ ዝርዝር ሰነድ መሃል ለይቼ በማዉጣት ለዛሬ የወያኔ የገበና ማሕደር የመረጥኩላችሁን ሰነድ እነሆ። የወያኔ ገባና መዘገባችን ያስፈራቸዉ ሁሉ ብርታቱን ይስጣችሁ እያልን መዘገባችን የምንቀጥል መሆናችነን ስንገልጽ በደስታ ነዉ። ከሰነዱ መግብያ እንጀምር፡ “የዛሬዉ “ማሌሊት”የቀድሞዉ የህወሓት “ኮሚኒስት” ሃይል የዉጭ መልኩ እንጂ ዉስጣዊ ገጽታዉ ምን እንደሚመስል የሚያዉቅ ሰዉ ጥቂት ነዉ። የማንኛዉም ነገር ወሳኝ መልኩ ዉስጣዊ ባሕሪዉ በመሆኑ ለዚያ ለዘመናት ሰላምና ዕድገት እርም ለሆነበት ሕዝባችን ስንል የዚህ ኮሚኒስት ሃይል ነኝ ባይ “ማሌሊት” ዉስጠ ባሕሪ ግልጽ ማድረግ ለትግሉ መፋፋም እጅግ የሚጠቅም በመሆኑ እንደ ታጋይ ይህን ለማድረግ ተገቢ ግዴታዉ ነዉ። “ማሌሊት” በዚያዉ ዘመናዊ መፈክሩ “ግልፅ መድረክ እንጠቀም፤ልዩነታችንን ሁሉም ይወቀዉ” በማለት ፉከራ ስለሚያበዛ በዚህ ጽሁፍ ላይ ቅን ስሜት እንደሚሰዉ የመነመነ ተስፋ አለኝ። የ “ማሌሊት” ወይም የህወሓት “ኮሚኒሰት” ሃይል ዉስጣዊ ማንነት ለማበጠር ብዙ ርዕስ ነገሮችን አንስቶ ለማብራራት የሚቻል ነዉ። ማሌሊትና ዲሞክራሲማሌሊት እና የሕብረት ግምባር ማሌሊት እና የኤርትራ ወያኔ፣ ማሌሊትና የጋራ መግለጫዎቹ፤ወዘተ…የሚሉ ርዕስ ነገሮች ገባጣ መስመሮቹን ለማብራራት ይቻላል። ለጊዜዉ ግን በዚህ የህወሓት ዕድል በራስ የመወሰን መብት ጉዳይ ማለትም በትግራይ ሕዝብ የብሔር ጥያቄ ላይ በማብራራት እንጀምር። ይልና-በአረጋዊ በርሔ እና “ማርከስ የማያዉቀዉ ላምፐን” ተብሎ በቅጽል ስሙ በሚታወቀዉ መለስ ዜናዊ እንዲሁም ሌሎቹ መስፍናዊ ብሔረተንነት የተጠናወታቸዉ የሚላቸዉ ስብሓት ነጋ እና አባይ ፀሃየ መካከል የነበረዉ የተለያዩ ድርጅቱን የሚመለከቱ ክርክሮች በስፋት ሲገልጽ፣ የትግራይ ሪፑብሊክ ምስረታ ዓላማ ማለትም መገንጠሉ ዓላማ ማን እንዳቀደዉ እና ያቀደዉ ክፍልም (3 ዋና የዕቅዱ ተላሚዎች እና ሌሎች 3 የነሱ ተባባሪዎች) ስለ ዕቅዱ ተጠይቆ የሰጠዉ መልስ እና ለምንስ እንደታቀደ ሁሉ በዝርዝር ያስቀምጥና፣ ይህ ጠባብ ቡድን ድርጅቱን በጠባብ ብሔረተኛነት ዓላማ ለማራመድ የተጠቀመባቸዉ ዘዴዎች እና መሰሪ ጎዳናዎች በስፋት ካብራራ በሗላ። እንዲሁም ድርጅቱ ለይስሙላ የሕብረት ትግል በማለት ሲያስተጋባዉ የነበረዉ ዉሸት እና መሰረታዊ የመብት ጥያቄዎች አንስተዉ ለጠየቁ የኢሕዴን/ብአዴን አባላት በተሓህት ባለስልጣናት በግል እየተጠሩ “ከፖሊስ መርመራ ባልተናናሰ ምርመራ እና ፍጥጫ” እየተደረገባቸዉ ለወደፊቱ የሚገለጽ ምስጢር በማለት በይደር ያስቆየዉ ሃተታ ከዘረዘረ በሗላ ያ ረዥም ትንተና እና የደርጅቱ ባሕሪ በስፋት ከተነተነ ካስቀመጠ በሗላ፣ ድረጅቱ በጠባብ ብሔረተኛነት እየተጓዘ በጸረ አማራ ቅስቀሳዉ እንዴት ይጓዝ እንደነበር ሰነዱ እስካሁን ድረስ ለሕዝብ ይፋ ከሆኑት ካነበብናቸዉ ከማናቸዉን ሰነዶች በላይ በማያሻማ ግልፅነት እንዲህ ሲል በግልጽ ያስቀምጠዋል። “… ከአንደኛዉ እስከ 2ኛዉ የሕወሓት ጉባኤ ድረስ ለእኩልነታዊ አንድነት ይሁን ለዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ምስረታ ቅድሚያ ሰጥቶ መታገል ወይም የሕብረት ትግል የሚፈጥርበት መንገድ መፈለግ የሚባል ጉዳይ አልነበረም ብንል ከሃቅ አንርቅም። በህወሓት በኩል የሕብረት ትግልን የማይጋብዙ አደናቀፊ አቀራረቦች ስለነበሩ ብቻ ነዉ። የሕብረት ትግሉ እንዳይፋጠን ብቻ ሳይሆን ይባስ ብሎ የተለያዩ ድርጅቶች ትምክህታዊ አመለካከት እግዶናል፣የሕብረተሰባችን ጠባብ መስፍናዊ አመለካካት የፈጠረዉ ችግር ነዉ”እየተባለ መደባዊ ወገናዊነት አበጥሮ የማይመለከት” “ፀረ አማራ” የሚል ቅስቀሳ ነበር። ባሕላዊ ትርኢቶች፣ትያትሮች፣ቀልዶች፣አባባሎች በዚህ ጠባብ መርዝ እየተለወሰ ቀርበዋል። በዚህ ድርጅት የሚቀርበዉ “ባሕላዊ ትርኢቶች” ጠባብ ብሔረተኝነት የሚያዳምቁ ብቻ ናቸዉ የማያሰኘን አደናጋሪ የሆኑ መደባዊ ወገንነት የሚያንፀባርቁና የሁሉም ጭቁን ኢትዮጵያዊ ጥያቄ የሚያዳምቁ የተለያዩ ዘፈኖች አሉ።ይህ ግን ባንድ ጠባብ ወይም ትምክሕታዊ ዘፈን የሚታይ፣ ድርጅቱ ለእዩልኝ ስሙልኝ የሚያቀርበዉ ማፊያዊ ፕሮፖጋንዳ ዘመቻ ነዉ። “ተራማጅ ነኝ፣ቀድሞዉንም ኮሚኒስት ነበርኩ” የሚለን የህወሓት ቡድን “ጠባብ ብሔረተኝነት የሚያስፋፋ ባሕላዊ ቅስቀሳ” ሲካሄድ “ዝም ብሎ ተመልክቷል” ብቻ ሳይሆን “ይበልጥ ይቀጥል” እያለ “የእደግ ተመንደግ” መመሪያዉን ዉስጥ ዉስጡን ይሰጥ ነበር። ትግላችን ጠባብ ባሕላዊ ቅስቀሳዎችን በሚመለከት የኢትዮጵያ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ (አህዴን) አባሎች በተደጋጋሚ ተቃዉሞ ያቀርቡ እንደነበር ጠቅሰን ዝርዝሩን እንተወዉ።ይህ የአመራር ቡድን “የዕደግ ተመንደግ” መመሪያዉን እየሰጠ የሚንቀሳቀስበት የራሱ ምክንያት አለዉ። ጠባብ ማኒፌስቶን አርሜአለሁ በሚልበት በዚያ በሆ-ሆየ ወቅት፣ጠባብ ብሔረተኝነትን ለማዳመቅ ስለከበደዉ ነዉ። ዞሮ ዞሮ ግን ከጠባብ ጓሮዉ ስለማይወጣ ጠባብ መመሪያዉ በግልጽ መዉጣት አይቀርለትም። በሗላ እንመለስበታለን። ከዚያ በረቂቅ መንገድ ከሚካሄዱት ጠባብ ብሔረተኝነት ቅስቀሳዎች አንድ ጠቅሰነዉ ልናልፍ የሚገባ አብነት አለ። አጼ ዮሐነስ እና አጼ ምኒልክ ግዛቶቻቸዉን ለማስፋፋት ሲሉ ህዝቡን እያተራመሱ ከባድ ቅራኔ አሳልፈዋል። ሁለቱም በሚፈጥሩት ትንቅንቅ በዚያ ሗላ ቀር ህብረተሰብ ዘንድ የሚንጸባረቅ ሁኔታ ሊኖር ነዉ። ተራማጆች እና ኮሚኒስቶች ለሕብረተሰብ ቆመናል ካሉ ደግሞ መሳፍንቶች በሕዝቦች መካከል ያደረሱት ክፍፍል እንዲጠፋ እና እንዲታረቅ ሊጥሩ ይገባል።ይህ የህወሓት ኮሚኒሰት ያመራር ቡድን ግን ያንን የስስት ምኞታቸዉን እንዲያገለግላቸዉ ስለሚፈልጉ በዚሁ ታሪክ ላይ ተንተርሰዉ “አማሮች የትግራይ ሕዝብ ደመኛ ጠላቶች ናቸዉ፣ከአማሮች ጋር መኖር እንዴት ይቻላል ወዘተ…” እያሉ ሲያስፋፉበት ይገኛሉ። የሚኒልክ ሰራዊት አለ ስንቅ ወደ ዓድዋ ጦርነት ስላዘመቱት የትግራይን ሕዝብ ንብረት አጠፉት የሚል ታሪካዊ ትምሕርትም አለ። ይህ አንድ ሐቅ ከሆነ ሌላዉ ሐቅ ደግሞ ከዚሁ ጋር መጠቀስ ነበረበት። ይህ ደግሞ የምኒልክ ሠራዊት ወደ ትግራይ ሲመጣ በአይሮፕላን ስላልነበረ ነፍጠኛ ሠራዊት እንደመሆኑ መጠን የሌላዉን አማራ ገበሬ ንብረትም ዘርፎት እንደመጣ ሊጠቀስ ይገባዉ ነበር። ሌላዉ ደግሞ በመጀመሪያዉ የወያኔ ታሪክ የማዕከላዊ ትግራይ ህዝብ በመሳፍንት ተመርቶ በደቡብ ትግራይ ህዝብ ላይ ከባድ ጥፋት አድርሷል። ይሁን እንጂ የትግራይ ህዝብ ብሔራዊ አንድነት እንዳይላላ እየተባለ ይህን የተከወነ ነገር ተረግጦ የሚታለፍበት ጊዜ ብዙ ስለሆነ ወደ መረሳቱ ደረጃ ተቃርቧል። ግሩም ነዉ። ታሪክ የማይታፈን እንኳ ቢሆንም ብሔራዊ አንድነትን ለማጠናከር ሲባል ደግሞ ከዚህ በበለጠ መደረግ ተገቢ አልነበረም? በተለይ ከማሌሊት መሪዎች። ጉዳዩ የሕዝቦች መሰረታዊ መደባዊ አንድነት አላልቶ ብሔራዊ ቅራኔ አሁን ካለበት በላይ እንዲቃረንና እንዲሾል በመሆኑ ያን ለጠባብ ዓላማዎቻቸዉ መገንቢያ እየመዘገቡና እያስተማሩ ያን መደባዊ ወገናዊነትን የሚያጎላዉን ግን ማላላትና መቅበር ግድ ሆኖባቸዋል።የዚህ ዓይነት ጠባብ ብሔረተኝነት የሚያስፋፋ ተግባር የሚቋረጥበትን መንገድ እንፈልግ ባልንበት ቁጥር በጥቃቅን ነገሮች ጊዜአችሁን ታባክናላችሁ ተብለን ተኮንነናል።” በማለት ዶ/ር አረጋዊ በርሔ የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ ዋና መስራች አባል እና የድርጅቱ የማአከላዊ አመራር አባል እና የድርጅቱ ወታደራዊ ኮሚቴ ዋና አዛዥ ስለ ድርጅቱ ጠባብ ብሔረተናነት እና ድብቅ ባሕሪዉ እና ተንኮል ከላይ እንዳነበባችሁት ገልጾታል። ትግሉ ይቀጥላል! ትግሉ ረዢም ቢሆንም በጠባብ ብሔረተኞች ሕሊና የሚጓዙ ግብዞች ከጊዜ ወደ ጊዜ እተጋለጡ ወደ አይቀሬዉ የመጨረሻዉ ዉድቀታቸዉ ያመራሉ። በጠባብ ብሔረተኛነት ስነ ልቦና ዜጎችን ቀስቅሰዉ መጠነ ሰፊ ጥፋት እና ጥላቻ ለፈጠሩት ሁሉ የጊዜ ጉዳይ እነጂ ተጠያቂነታቸዉ አይቀሬ ነዉ።ጉዞአችን ረዢም ቢሆንም ድሉ የማይቀር ነዉ። በአንድነታችን ላይ ጥላቻና መራራቅ የፈጠሩ የህወሓት መሪዎች በዓለም አቀፍ ሕግ ወይንም በዉጭ አገሮች ፍርድ ቤቶች እንዲከሰሱ ኢትዮጵያዉያን የሕግና እንዲሁም የማሕበራዊ ኑሮ ባለሞያዎች ቋሚ የሞያተኞች ማሕበር መስርተዉ በሙያቸዉ ስለሰለባዎች ፍትሕ ማስገኘት ጉዳይ ቢጥሩና ፖለቲካዉ ዉስጥ የዕረጎ ዝምብ እየሆኑ ሓምሳ ገጽ ከመጻፍ በሙያቸዉ ቢሰሩ በንጹሃን ደም እያሾፉ ያሉትን ወንጀለኞች ሁሉ ተጨማሪ ዕልቂትን ትርምስን ለወደፎቱ ከምያመጡ ከማዳን በላይ ጠባብ ብሔረተኞች ዛሬም እየቀጠለበት ያለዉ የሰብአዊ ሕይወትንና ሰብአዊ መብት መረገጥን ከመቀጠል ማስቆም ይችላሉ። በዚህ ላይ አዲስ የትግል ምዕራፍ እንዲጀመር ለሰባዊ መብት የቆሙ የሕግ ባለሞያዎች ሁሉ እንዲወያዩበት አሳስባለሁ። የሰብአዊ ረገጣ እንደዋዛ እንዲታይ እና የሰለባዎች ጥቃት ዛሬ ሳይሆን “ዓረና የተባለ ፓርቲ” ወደ መንግሥትነት ሲመጣ ክሳችሁን አስሰሙ የሚሉን የዘመኑ ፖለቲከኞች ሁሉ እነሱ ቁልቁል በተያያዙት የማራቶን የሗሊት ሩጫ እንዳያስገቡን ሁሉም በያለበት አንደዘወትሩ ከመቸዉም በበለጠ የፖለቲካ ኪሳራቸዉን እንዲያጋልጣቸዉ በዚህ አጋጣሚ አደራየ እንደጥንቱ ደግሜ ሁሉም ጆሮዉን ያቁም ዓይኑን ይክፈት። ለመዉሰድ እያቀዱን ያሉትን ጉዞ አደገኛ እና የሗሊት ፖለቲካ ጨዋታቸዉን ላለመጫወት ነቅቶ ሁሉም ዘብ ይቁም! ወደ መጨረሻዉ እየተቃረብን ስለሆነ ትግሉ እየመረረ መልክ እያጣ ማን ማን እንደሆነ ወገን የሚለይበት እርከን ስለደረስን ብንበታተንም በቁርጠኝነት ከመነሻ ዓላመችን ሳንዛነፍ ለሰለባዎችና ለፍትሕ ቆመን አገርን ለመገነጣጠል የፈሽስትና የኮሚኒስት የግንጠላ መመሪያ አንግበዉ ተመልሰዉ ከተተፉበት ትግል አንሰራርተዉ በመቆም ሳያሟሉት የቀሩት ግንጠላ ከተቀሩ ገንጣይ ጓዶቻቸዉ ጋር ድብቅ ስራቸዉን ለሟሟላት ትግሉን ለመጥለፍ እያጋገሙ ያሉትን የታሪክ እንክርዳዶችን ብልጠቱን እንንፈጋቸዉ። የከፋ ቀን ሲመጣባቸዉ እነ ገብሩ እና እነ ስየ እነ አዉዓሎም ወገንተኝነታቸዉ ከነ መለስ እንጂ ከእኛ ጋር እንደማይሆኑ ለደቂቃም ቢሆን አትጠራጠሩ። የኮሚኒስቶች/ፋሽስቶች የግንጠላ ፖሊሲ ለኢትዮጵያ ግጭት አንጂ አንድነትን አያመጣም! ጌታቸዉ ረዳ http://www.ethiopiansemay.blogspot.com